የብቸና ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ልዑካን ቡድን በደብረ ማርቆስ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የስራ ልምድ ልውውጥ ጉብኝት አካሄዱ፡፡
#DMPTC ነሐሴ 7/ 2018 ደብረ ማርቆስ
የብቸና ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ዲኖችን ጨምሮ የተለያዩ የስራ ሀላፊዎችን ያካተተ የልዑካን ቡድን በኮሌጃችን ያለውን የስራ እንቅስቃሴ ለመመልከት እንዲሁም ያለውን ተሞክሮ ለመውሰድ የሚያስችላቸውን የስራ ልምድ ልውውጥ በኮልጁ አካሂደዋል::
ልዑካን ቡድኑ በኮሌጃችን በነበረው የልምድ ልውውጥ መርሃ-ግብር ወቅትም የደብረ ማረቆስ ፖሊቴክኒክ በተቋም ደረጃ እየሰራቸዉ ያሉ ስራዎችን በዝርዝር የተመለከቱ ሲሆን ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ በተደረገላቸው አቀባበልና በተመለከቱት የኮሌጁ እንቅስቃሴ መነሻ በማድረግ የደብረ ማርቆስ ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ እያከናወናቸው የሚገኙ ዘርፈ ብዙ የስራ እንቅስቃሴዎች በጣም ጥሩ መሆናቸውን ገልፀው በዚህም ኮሌጁ ከጀመረዉ ውጤታማ ጉዞ ብዙ ልምዶችን መቅሰም መቻላቸውንም ገልፀዋል::
በተጨማሪም ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ የስልጠና ዎርክ ሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በነበራቸው የልምምድ ልውውጥ መርሃ-ግብርም የተሳካ ቆይታን በኮሌጃችን ማድረግ ችለዋል::
ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት አማራጮች ያግኙ፡-
በቴሌግራም፡- https://telegram.me/dmtvet1990
በፌስቡክ ፔጃችንን ፡-https://m.facebook.com/Debre-Markos-Poly-Technic-College-
በድረ ገጽ ፡ www.https://dmptc.edu.et/